መዝሙር 137
ታማኝ ሴቶች፣ ክርስቲያን እህቶች
(ሮም 16:2)
-
1. ሣራና አስቴር፣ ማርያም፣ ሩት፣ ሌሎችም፣
ጎበዝ ሴቶች፣ ታማኝ ሚስቶች ነበሩ፤
ከምንም በላይ ለአምላክ ያደሩ።
እነዚ’ን ታማኞች በስም አውቀናል፤
ግን ስማቸው ባይሰፍርም በቃሉ፣
ሞገሱን ያገኙ ብዙ ሴቶች አሉ።
-
2. ታማኞችና ደፋሮችም ናቸው፤
ጥሩነትና ደግነት ያላቸው።
መልካም ባሕርያቸው ነው መለያቸው።
ጥሩ ምሳሌ ሆኑ ለሁሉም ሰው።
እነሱን የምትመስሉ እህቶች፣
መልካም ባሕርያችሁ ይጠቅማል ለሌሎች።
-
3. እናት፣ እህት፣ ሚስትና መበለቶች
ድርሻቹን በደስታ ትወጣላችሁ።
ልከኞች ናችሁ፣ ከልብ ’ምትገዙ፤
አትፍሩ ሞገሱን ስላገኛችሁ።
ውድ እህቶቻችን በሉ በርቱ፤
ይሖዋ ያጽናችሁ፤ ቀርቧል ሽልማቱ።
(በተጨማሪም ፊልጵ. 4:3ን፣ 1 ጢሞ. 2:9, 10ን እና 1 ጴጥ. 3:4, 5ን ተመልከት።)