መዝሙር 41
እባክህ ጸሎቴን ስማ
(መዝሙር 54)
-
1. ይሖዋ ’ባት፣ እባክህ ስማኝ።
አምላኬ ነህ፤ እኔም ያንተ ነኝ።
ስምህ ታላቅ፣ ወደር ’ማያገኝ።
(አዝማች)
ደጉ አምላኬ፣ ’ባክህ ስማኝ።
-
2. ላመስግንህ ለዛሬዋ ቀን።
ሕይወት ሰጥተህ፣ መራህ መንገዴን።
ደስ ብሎኛል፣ በእቅፍህ ነኝ።
(አዝማች)
ደጉ አምላኬ፣ ’ባክህ ስማኝ።
-
3. እጓጓለሁ መልካም ማድረግን።
ምራኝ ልሂድ፣ በአንተ ብርሃን።
ችግሮቼን ልቋቋም እርዳኝ።
(አዝማች)
ደጉ አምላኬ፣ ’ባክህ ስማኝ።