በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

መዝሙር 92

ለስምህ የሚሆን ቤት

ለስምህ የሚሆን ቤት

(1 ዜና መዋዕል 29:16)

  1. 1. አምላክ ሆይ፣ ለስምህ ቤት መሥራት፣

    ክብር ነው የማይገኝ መብት!

    ይህን ቤት ሰጠንህ በደስታ፤

    ክብርህ ይናኝ በዚህ ቦታ።

    ላንተ ’ምንሰጥህ ሁሉም ነገር፣

    ቀድሞም ቢሆን ያንተ ነበር።

    ንብረት፣ ችሎታ፣ ኃይላችንን

    ሳንቆጥብ እንሰጥሃለን።

    (አዝማች)

    ይህን ቤት ላንተ ሰጠንህ፤

    እንዲጠራበት ስምህ።

    ለአገልግሎትህ ይዋል፤

    ተቀበለን እባክህ።

  2. 2. ይሖዋ ሆይ፣ እናወድስህ፤

    በክብርህ ይሞላ ቤትህ።

    ሕዝቦች ይምጡ፣ ይወቁ አንተን፤

    ግርማህም ይበልጥ ከፍ ይበል።

    ቤቱን ላምልኮህ ወስነናል፤

    መንከባከብ ይገባናል።

    ጸንቶ ’ንዲኖር እንመኛለን፤

    ድጋፍ ሆኖ ለሥራችን።

    (አዝማች)

    ይህን ቤት ላንተ ሰጠንህ፤

    እንዲጠራበት ስምህ።

    ለአገልግሎትህ ይዋል፤

    ተቀበለን እባክህ።

(በተጨማሪም 1 ነገ. 8:18, 27⁠ን፣ 1 ዜና 29:11-14⁠ን እና ሥራ 20:24⁠ን ተመልከት።)