መዝሙር 143
ነቅተን በተስፋ እንጠብቃለን
-
1. ጊዜን፣ ወቅትን ’ሚለውጠው
አምላካችን ይሖዋ ነው።
በጣም ቀርቧል የቁጣው ቀን፤
ይህን እርግጠኞች ነን።
(አዝማች)
ነቅተን በተስፋ እንጠብቃለን፤
ያምላክ ዓላማ ሲፈጸም
ለማየት እንጓጓለን።
-
2. አምላክ ጊዜውን ወስኗል፤
ክርስቶስም ተዘጋጅቷል።
በቅርብ እርምጃ ይወስዳል፤
ታላቅ ድል ይቀዳጃል።
(አዝማች)
ነቅተን በተስፋ እንጠብቃለን፤
ያምላክ ዓላማ ሲፈጸም
ለማየት እንጓጓለን።
-
3. ፍጥረት በጭንቅ ቢቃትትም
እምነት አለን፤ ተስፋ ’ንቆርጥም።
ታላቁ ያምላክ ቀን ቀርቧል፤
ፍጥረት ነፃ ይወጣል።
(አዝማች)
ነቅተን በተስፋ እንጠብቃለን፤
ያምላክ ዓላማ ሲፈጸም
ለማየት እንጓጓለን።