በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

መዝሙር 23

ይሖዋ መግዛት ጀምሯል

ይሖዋ መግዛት ጀምሯል

(ራእይ 11:15)

  1. 1. የአምላክ ልጅ ይወደስ፤

    መንግሥቱ ተቋቁሟል፤

    ከጽዮን ሆኖ መግዛት ጀምሯል።

    ከፍ እና’ርግ ድምፃችንን፤

    እንዘምር ላምላካችን።

    ዙፋኑን ይዟል

    ክርስቶስ አዳኛችን።

    (አዝማች)

    ምን ያመጣል የአምላክ መንግሥት?

    የጽድቅና የ’ውነትን ድል።

    ምን ያስገኛል የአምላክ መንግሥት?

    ሰላም፣ ደስታ፣ ፍጹም ሕይወት።

    ታማኝ ፍቅሩን ስላሳየን

    ይሖዋ ’ባት ይመስገን።

  2. 2. ክርስቶስ ሥልጣን ይዟል፤

    አርማጌዶንም ቀርቧል።

    የሰይጣን ዓለም በቅርብ ይጠፋል።

    ብዙዎች ስላልሰሙ

    ምሥራቹን አስፋፉ፤

    እርዷቸው ቅኖች

    ካምላክ ጎን ይሰለፉ።

    (አዝማች)

    ምን ያመጣል የአምላክ መንግሥት?

    የጽድቅና የ’ውነትን ድል።

    ምን ያስገኛል የአምላክ መንግሥት?

    ሰላም፣ ደስታ፣ ፍጹም ሕይወት።

    ታማኝ ፍቅሩን ስላሳየን

    ይሖዋ ’ባት ይመስገን።

  3. 3. ንጉሡን ’ናወድሰው፤

    ታላቅና ድንቅ ነው።

    በአምላክ ስም መጥቷል እናክብረው።

    ሁሉን የሚገዛበት ቀን

    በጣም በመቅረቡ፣

    ወዳምላክ ቤት ግቡ

    ሞገሱን ለምኑ።

    (አዝማች)

    ምን ያመጣል የአምላክ መንግሥት?

    የጽድቅና የ’ውነትን ድል።

    ምን ያስገኛል የአምላክ መንግሥት?

    ሰላም፣ ደስታ፣ ፍጹም ሕይወት።

    ታማኝ ፍቅሩን ስላሳየን

    ይሖዋ ’ባት ይመስገን።

(በተጨማሪም 2 ሳሙ. 7:22⁠ን፣ ዳን. 2:44⁠ን እና ራእይ 7:15⁠ን ተመልከት።)