በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ምዕራፍ 33

የአምላክ መንግሥት ምን ነገሮችን ያከናውናል?

የአምላክ መንግሥት ምን ነገሮችን ያከናውናል?

የአምላክ መንግሥት መግዛት ጀምሯል። በቅርቡ በምድር ላይ ሥር ነቀል ለውጦችን ያደርጋል። እስቲ በአምላክ መንግሥት አገዛዝ ሥር የምታገኛቸውን አንዳንድ በረከቶች እንመልከት።

1. የአምላክ መንግሥት በምድር ላይ ሰላምና ፍትሕ እንዲሰፍን የሚያደርገው እንዴት ነው?

የአምላክ መንግሥት ንጉሥ የሆነው ኢየሱስ በአርማጌዶን ጦርነት ላይ ክፉ ሰዎችንና መንግሥታትን ያጠፋል። (ራእይ 16:14, 16) በዚያ ወቅት “ለጥቂት ጊዜ ነው እንጂ ክፉዎች አይኖሩም” የሚለው የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢት ሙሉ በሙሉ ይፈጸማል። (መዝሙር 37:10) ኢየሱስ በአምላክ መንግሥት አማካኝነት በመላዋ ምድር ላይ ሰላምና ፍትሕ እንዲሰፍን ያደርጋል።—ኢሳይያስ 11:4⁠ን አንብብ።

2. የአምላክ ፈቃድ በምድር ላይ በሚፈጸምበት ጊዜ ምን ዓይነት ሕይወት ይኖረናል?

በአምላክ መንግሥት አገዛዝ ሥር “ጻድቃን ምድርን ይወርሳሉ፤ በእሷም ላይ ለዘላለም ይኖራሉ።” (መዝሙር 37:29) ክፉዎች በሌሉበት እንዲሁም ይሖዋን የሚወዱና እርስ በርስ የሚዋደዱ ሰዎች ብቻ ባሉበት ዓለም ውስጥ መኖር ምን ያህል አስደሳች እንደሚሆን እስቲ አስበው! በሕመም የሚሠቃይ ሰው አይኖርም፤ ሁሉም ሰው ለዘላለም ይኖራል።

3. ክፉዎች ከጠፉ በኋላ የአምላክ መንግሥት ምን ነገሮችን ያከናውናል?

ክፉዎች ከጠፉ በኋላ ኢየሱስ ለ1,000 ዓመት ያህል ንጉሥ ሆኖ ይገዛል። በዚያ ወቅት ኢየሱስና አብረውት የሚገዙት 144,000 ገዢዎች፣ ሰዎች ፍጹምና ከኃጢአት ነፃ እንዲሆኑ ይረዳሉ። የሺህ ዓመቱ ግዛት መጨረሻ ላይ ምድር የይሖዋን ሕጎች በሚታዘዙ ደስተኛ ሰዎች የተሞላች ውብ ገነት ትሆናለች። ከዚያም ኢየሱስ መንግሥቱን ለአባቱ ለይሖዋ ያስረክባል። የይሖዋ ስም ከዚህ በፊት ሆኖ በማያውቅ መንገድ ‘ይቀደሳል።’ (ማቴዎስ 6:9, 10) ይሖዋ ለተገዢዎቹ የሚያስብ ጥሩ ገዢ እንደሆነ ይረጋገጣል። ከዚያም ይሖዋ ሰይጣንንና አጋንንቱን ጨምሮ በእሱ አገዛዝ ላይ የሚያምፁትን ሁሉ ያጠፋል። (ራእይ 20:7-10) የአምላክ መንግሥት የሚያመጣቸው በረከቶች ለዘላለም ይቀጥላሉ።

ጠለቅ ያለ ጥናት

አምላክ የወደፊቱን ጊዜ አስመልክቶ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሰጣቸውን ተስፋዎች በሙሉ በመንግሥቱ አማካኝነት እንደሚፈጽም እርግጠኛ መሆን የምንችለው ለምን እንደሆነ እንመለከታለን።

4. የአምላክ መንግሥት የሰዎችን አገዛዝ ያስወግዳል

“ሰው ሰውን የገዛው ለጉዳቱ ነው።” (መክብብ 8:9) ይሖዋ በፍትሕ መጓደል ምክንያት የተከሰቱ ችግሮችን በመንግሥቱ አማካኝነት ያስተካክላል።

ዳንኤል 2:44ን እና 2 ተሰሎንቄ 1:6-8ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተሉት ጥያቄዎች ላይ ተወያዩ፦

  • ይሖዋና ልጁ ኢየሱስ ሰዎች በሚያስተዳድሯቸው መንግሥታትና በደጋፊዎቻቸው ላይ ምን እርምጃ ይወስዳሉ?

  • ስለ ይሖዋና ስለ ኢየሱስ የተማርከው ነገር እነሱ የሚወስዱት እርምጃ ትክክለኛና ፍትሐዊ እንደሆነ እንድትተማመን የሚያደርግህ እንዴት ነው?

5. ኢየሱስ ከሁሉ የተሻለ ንጉሥ ነው

ኢየሱስ የአምላክ መንግሥት ንጉሥ እንደመሆኑ መጠን በምድር ላይ ላሉ ተገዢዎቹ ብዙ ጠቃሚ ነገሮችን ያከናውናል። ኢየሱስ ከዚህ በፊት ያደረጋቸው ነገሮች እንዲህ ለማድረግ ፍላጎቱ እንዳለውና አምላክም ኃይል እንደሰጠው ያሳያሉ። ይህን የሚያሳዩ አንዳንድ ምሳሌዎችን ቪዲዮው ላይ ተመልከቱ

ኢየሱስ ምድር ላይ በነበረበት ጊዜ የአምላክ መንግሥት ወደፊት የሚያከናውናቸውን ነገሮች በጥቂቱም ቢሆን አሳይቷል። አንተ በግልህ እዚህ ላይ ከተዘረዘሩት ነገሮች መካከል የትኛው ሲፈጸም ለማየት ትጓጓለህ? ከእያንዳንዱ ተስፋ ጋር አብረው የተጠቀሱትን ጥቅሶች አንብቡ።

ኢየሱስ ምድር ላይ ሳለ . . .

ኢየሱስ ከሰማይ ሆኖ . . .

  • በፕላኔቷ ምድራችን ላይ የደረሰውን ጉዳት ያስተካክላል።—ኢሳይያስ 35:1, 2

6. የአምላክ መንግሥት ወደፊት አስደሳች ጊዜ ያመጣል

የአምላክ መንግሥት ይሖዋ ለሰው ልጆች ያለው የመጀመሪያ ዓላማ ሙሉ በሙሉ እንዲፈጸም ያደርጋል። ሰዎች ገነት በሆነች ምድር ላይ ለዘላለም ይኖራሉ። ይሖዋ በልጁ በኢየሱስ አማካኝነት ዓላማውን ዳር ለማድረስ እየሠራ ያለው እንዴት እንደሆነ ለማየት ቪዲዮውን ተመልከቱ

መዝሙር 145:16ን አንብቡ፤ ከዚያም በሚከተለው ጥያቄ ላይ ተወያዩ፦

  • ይሖዋ ‘የሕያዋን ፍጥረታትን ሁሉ ፍላጎት እንደሚያሟላ’ ማወቅህ ምን ስሜት ያሳድርብሃል?

አንዳንዶች እንዲህ ይላሉ፦ “ሁላችንም ተባብረን ከሠራን የዓለማችንን ችግሮች ማስወገድ እንችላለን።”

  • ሰዎች ከሚያስተዳድሯቸው መንግሥታት አቅም በላይ የሆኑ ሆኖም የአምላክ መንግሥት የሚያስወግዳቸው ችግሮች የትኞቹ ናቸው?

ማጠቃለያ

የአምላክ መንግሥት ዓላማውን ዳር ያደርሳል። መላዋ ምድር ይሖዋን ለዘላለም በሚያመልኩ ጥሩ ሰዎች እንድትሞላና ገነት እንድትሆን ያደርጋል።

ክለሳ

  • የአምላክ መንግሥት የይሖዋ ስም እንዲቀደስ የሚያደርገው እንዴት ነው?

  • የአምላክ መንግሥት በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኙት ተስፋዎች እንዲፈጸሙ እንደሚያደርግ መተማመን የምንችለው ለምንድን ነው?

  • የአምላክ መንግሥት ከሚያመጣቸው በረከቶች መካከል አንተ ለማየት የምትጓጓው የትኛውን ነው?

ግብ

ምርምር አድርግ

‘አርማጌዶን’ የሚለው ቃል ምን ያመለክታል?

“የአርማጌዶን ጦርነት ምንድን ነው?” (ድረ ገጻችን ላይ የወጣ ርዕስ)

በኢየሱስ የ1,000 ዓመት ግዛት ወቅት እንዲሁም በዚህ ግዛት መጨረሻ ላይ ምን ነገሮች ይከናወናሉ?

“በፍርድ ቀን ምን ነገሮች ይከናወናሉ?” (መጠበቂያ ግንብ መስከረም 1, 2012)

የአምላክ መንግሥት ወደፊት በሚያመጣቸው በረከቶች ላይ በቤተሰብ አንድ ላይ ሆኖ ማሰላሰል የሚቻለው እንዴት ነው?

በገነት ውስጥ ስትኖር ይታይህ (1:50)

“አእምሮዬን የሚረብሹ ብዙ ጥያቄዎች ነበሩኝ” በሚለው ርዕስ ሥር ዓማፂ የነበረ አንድ ሰው ለጥያቄዎቹ መልስ ያገኘው እንዴት እንደሆነ ተመልከት።

“መጽሐፍ ቅዱስ የሰዎችን ሕይወት ይለውጣል” (መጠበቂያ ግንብ ጥር 1, 2012)